# | amh | eng |
---|
1 | የኢትዮጵያ ዞን ፱ ጦማሪያን የአለምአቀፍ ህግ ድክመቶች ተጋርጦባቸዋል | Ethiopia's Zone9 Bloggers Face the Limits of International Law |
2 | የዞን ፱ አባላት አብረው አዲስ አበባ ውስጥ ሳሉ፣ እ. ኤ. | Zone9 members together in Addis Ababa, 2012. |
3 | አ. 2012 ዓ. | Photo used with permission. |
4 | ም. ። ፎቶ ጥቅም ላይ ለማዋል ፍቃድ ተሰጥቷል። | This post was jointly published with the World Policy Journal blog. |
5 | ይህ ልጥፍ ከWorld Policy Journal ጦማር ጋር በመተባበር የታተመ ነው። | |
6 | የአለምአቀፍ ሰብዓዊ መብቶች ስርዓት የተሰናከለ ነው - እንዲያውም መጀመሪያውኑ ሰርቶ ላያውቅ ይችላል። | The international human rights system is broken - or perhaps it never worked at all. |
7 | በብዙ ጉዳዮች ላይ እንደታየው ከሆነ የዜጎች ሰብዓዊ መብቶች በየአገራቸው ብሔራዊ ህጎች ይጣሳሉ፣ ምንም እንኳ በተባበሩት መንግስታት ሁለገብ አዋጅ (United Nations' Universal Declaration)፣ እና በአውሮፓ የደህንነት እና የትብብር ድርጅት፣ በየአሜሪካ አገራት ድርጅት፣ በአፍሪካ ኮሚሽን እና በሌሎች ውስጥ ያሉ ቃል የተገባባቸው የአለምአቀፍ ሰብዓዊ መብቶች ቢያካትቱም። | In case after case, citizens' human rights are violated under the national laws of their respective countries, despite the existence of international human rights commitments in the United Nations' Universal Declaration, and by the Organization for Security and Cooperation in Europe, the Organization of American States, the African Commission, and others. |
8 | የአለምአቀፍ ወንጀል ፍርድ ቤቱ አይን ካወጡት በስተቀር ማንኛውም የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በተመለከተ ማድረግ የሚችለው ነገር የለም፣ እና አባል አገራት ፍትህ በመሠላቸው መልኩ የመስጠት ሰፊ ነጻነት አላቸው። | The International Criminal Court has little say concerning any but the most egregious of international human rights violations, and member states have wide latitude to dispense justice as they see fit. |
9 | ሐሳብን የመግለጽ መብትን የሚጠብቁ የገዛ ህጎቻቸውን ማክበር ወይም ማስፈጸም ባልቻሉ አገሮች ውስጥ ለሚኖሩ ሰዎች አለምአቀፍ መርሖዎች እውነተኛ መፍትሔ ቢሰጣቸውም ከስንት አንዴ ነው። | For those who live in countries that fail to provide or enforce their own laws protecting freedom of expression, international principles have rarely provided actual recourse. |
10 | ዛሬ ዞን ፱ ተብሎ በሚታወቀው ነጻ የኢትዮጵያውያን ጦማሪያን ቡድን ላይ እየሆነ ያለውም ይኸው ነው። | Today, this is the case with the independent Ethiopian blogger collective known as Zone9. |
11 | ባለፈው ዓመት ሚያዝያ ውስጥ የኢትዮጵያ መንግስት ስድስት የዞን ፱ አባላትን ሶስት ቅርበት ካላቸው ጋዜጠኞች ጋር በአዲስ አበባ ውስጥ አስሯል። | In April of this year, the government of Ethiopia arrested six members of Zone9 along with three affiliated journalists in Addis Ababa. |
12 | ምንም ክስ ሳይመሰረትባቸው ለወራት የተያዙ ሲሆኑ ከሌሎች ጋር እንዳይገናኙም ተከልክለዋል። | They were held for months without a formal charge and were denied the ability to communicate. |
13 | ሐምሌ ላይ ከእስር ቤት የወጣው የበፍቃዱ ኃይሉ ማስታወሻ እና እንዲሁም በፍርድ ቤት ውስጥ የተሰጡ ቃሎች በደል እና ተደጋጋሚ ድብደባዎች እንደደረሰባቸው ያስረዳሉ። | Testimony from Befeqadu Hailu, one of the accused bloggers who was smuggled out of prison in August, as well as statements in court, allege mistreatment and frequent beatings. |
14 | እነዚህ ዘጠኝ ሰዎች «የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እንደሆኑ ከሚያስመስሉ የውጪ ድርጅቶች ጋር አብሮ በመስራት…በማህበራዊ ገጾች በኩል የሕዝብ አመጽ ለማነሳሳት ገንዘብ ተቀብለዋል» በሚሉ ውንጀላዎች ተይዘዋል። | Informally, the nine were held on accusations of “working with foreign organizations that claim to be human rights activists and…receiving finance to incite public violence through social media.” |
15 | ሐምሌ ላይ የዞን ፱ እስረኞች መንግስት በይፋ አሸባሪዎች ብሎ ከሰየማቸው የፖለቲካ ተቃዋሚ ድርጅቶች ድጋፍ በመቀበል እና በአለምአቀፍ ተሟጋቾች ታክቲካል ቴክኖሎጂ ኮሌክቲቭ (Tactical Technology Collective) ከተባለው ጋዜጠኞች እና ተሟጋቾች እራሳቸውን ከዲጂታል ክትትል እንዲጠብቁ ከሚያግዛቸው ቡድን በኢሜይል ኢንክሪፕሽን እና ዳታ ሴኩሪቲ ስልጠና በመቀበል በ2001 ኢትዮጵያ ጸረ-ሽብር አዋጅ ተከስሰዋል። | In July, the Zone9 prisoners were charged under Ethiopia's Anti-Terrorism Proclamation of 2009 for receiving support from political opposition organizations, defined formally by the government as terrorists, and receiving training from international activists in email encryption and data security from the Tactical Technology Collective, a group that helps journalists and activists protect themselves from digital surveillance. |
16 | የዞን ፱ ጦማሪያን በቅርብ ጊዜ በነበረው የአረብ አመጾች ላይ እና በኢትዮጵያ ውስጥ ሊከሰቱ በሚችሉ ተመሳሳይ አመጾች የዘገበው እስክንድር ነጋን ጨምሮ በተመሳሳይ ህጎች ከተነጣጠሩ ሌሎች የሚዲያ ድምጾች ጋር ተቀላቅለዋል። | The Zone9 bloggers joined other media outlets targeted under similar laws, including Eskinder Nega, who had reported on recent Arab uprisings and the possibility of similar uprisings taking place in Ethiopia. |
17 | በቁጥጥር ስር ውሎ በ«ሽብርን በማቀድ፣ ዝግጅት በማድረግ፣ በማሴር፣ በማሳመጽ እና ሙከራ በማድረግ» ተከስሶ የ18 ዓመት እስር ተፈርዶበታል። | He was arrested and charged with the “planning, preparation, conspiracy, incitement and attempt” of terrorism and sentenced to 18 years in prison. |
18 | የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ያደረጓቸው አለምአቀፍ ስሞታዎች በጉዳዩ ላይ ተጽዕኖ አልነበረውም። | International appeals from human rights advocacy organizations have had little effect on the case. |
19 | ግንቦት ላይ የተባበሩት መንግስታት ከፍተኛ ኮሚሽነር ናቪ ፒሌይ እንዲህ ብላ የሚያብራራ ቃል ሰጥታለች፣ | In May, UN High Commissioner for Human Rights Navi Pillay issued a statement explaining, |
20 | በሽብርተኝነት ላይ የሚደረገው ዘመቻ ጋዜጠኞችን፣ ጦማሪያንን፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችን እና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አባላትን ለማስፈራራት እና ድምጽ ለማጥፋት እንደ ሰበብ ሆኖ ሊቀርብ አይችልም። | The fight against terrorism cannot serve as an excuse to intimidate and silence journalists, bloggers, human rights activists and members of civil society organizations. |
21 | እና ደግሞ ከውጪ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች ጋር አብሮ መስራት እንደ ወንጀል ተደርጎ ሊቆጠር አይገባም። | And working with foreign human rights organizations cannot be considered a crime. |
22 | በተጨማሪም፣ ሰባት የአለምአቀፍ ሰብዓዊ መብቶች እና የፕሬስ ነጻነት ድርጅቶች በላኩት አስቸኳይ ጥያቄ የአፍሪካ ኮሚሽን እና የተባበሩት መንግስታት በዞን ፱ ላይ በተከፈተባቸው ጉዳይ ላይ ጣልቃ እንዲገቡ ጠይቀዋል። | Additionally, seven international human rights and press freedom organizations pressed the African Commission and the United Nations in an urgent appeal to intervene in the case against Zone9. |
23 | ጥያቄው ጉድለት ባለው የክሶቹ ግልጽነት እና ተከሳሾቹ በቂ የህግ ምክር የማግኘት መብት ላይ ያተኮረ ነው። | The appeal focused on the lack of clear charges and failure to allow the defendants adequate legal representation. |
24 | የሚዲያ ህግ መከላከያ ተነሳሽነት (Media Legal Defence Initiative) ጠበቃ እና የጥያቄው መሪ ፈራሚ የሆነችው ናኒ ጃንሰን በኢሜይል ውስጥ ሁለቱም የአፍሪካ ኮሚሽን እና ተመድ «በእነዚህ ጉዳዮች ቀዳሚ ደረጃዎች ላይ በሚስጥራዊነት ስም ነው የሚሰሩት» ብላ ጽፋለች። | Nani Jansen, a lawyer for the Media Legal Defence Initiative and the lead signatory in the appeal, writes in an email that both the African Commission and the UN “operate under the cover of confidentiality in the early stages of these matters.” |
25 | እንዲህ ብላ ትቀጥላለች፦ | She continues: |
26 | ከአንድ መንግስት ጋር አንድ ጉዳይ ሲከታተሉ የውጪውን ዓለም ሳያሳውቁ ነው። | When they follow up with a Government, this is done without informing the outside world. |
27 | ብዙ ወራት (አብዛኛው ጊዜ ከዓመት በላይ) ካለፉ በኋላ ብቻ ነው ከአንድ መንግስት ጋር የተደረጉት እነዚህ ልውውጦች ለበላይ አካሉ በሚደረገው የእንቅስቃሴ ስልት ሪፖርት ላይ የሚታተመው። | Only months and months (often over a year) later, these exchanges with a Government get published in the mechanism's report to its supervisory body. |
28 | ስለዚህም፣ ማንኛውም ጣልቃ መግባት ዞን ፱ በሚወክለው የድምጽ ማፈኛ ስርዓት ውስጥ ይገባል-ከሕዝባዊ እይታ ወይም ተሳትፎ ተደብቆ። | Thus any intervention joins the rest of those in the cone of silence that is Zone9-hidden from public scrutiny or participation. |
29 | እነዚያ አካላት ጉዳዩን ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ቢከታተሉትም እንኳ ያላቸው አማራጭ የተገደበ ነው። | Even if these bodies do follow up with the Ethiopian government, their recourse is limited. |
30 | በአስቸኳይ ጥያቄው ላይ በጻፈችው ጽሑፍ ጃንሰን የአፍሪካ ኮሚሽን እስራቶቹን በአቋም ማውገዝ እንደሚችሉ፣ የሁለቱም ድርጅቶች ሪፖርት ጸሐፊዎች ምርመራ ለማካሄድ ወደ ኢትዮጵያ ኦፊሴላዊ ጉብኝቶችን እንዲያደርጉ መጠየቅ እንደሚችሉ፣ እና ኢትዮጵያ የተመድ ሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት አባል እንደመሆኗ መጠን እንደዚህ ያለ ጥያቄ የማክበር ግዴታ እንዳለባት አውስታለች። | In an article on the urgent appeal, Jansen notes that the African Commission can condemn the arrests in a resolution, that both organizations' rapporteurs can request official visits to Ethiopia to investigate, and that Ethiopia, as a member of the UN Human Rights Council, would be obligated to honor such a request. |
31 | ነገር ግን እንደዚህ ያሉ ጥያቄዎች ቢቀርቡ እና መርመራዎች ቢካሄዱም እንኳ ሊገኙ ይችላሉ ተብሎ የሚገመቱት ውጤቶች በኢትዮጵያ መንግስት ላይ የማስፈጸም ዕድሉ በጣም አነስተኛ ነው። | But even should such requests be made, and investigations conducted, there is little chance of enforcement of hypothetical findings on the Ethiopian government. |
32 | ጥያቄው ከቀረበበት ጊዜ ጀምሮ የኢትዮጵያ መንግስት በተከሳሾቹ ላይ በክሱ እንደቀጠለበት ነው። | Since the appeal, the Ethiopian government has proceeded with charges against the accused. |
33 | በችሎቱ ላይ ያሉ የቅርብ ጊዜ መረጃዎች ለተከሳሾቹ ቅርብ በሆኑ ወዳጆች በሚሄድ የችሎት መከታተያ ጦማር (Trial Tracker Blog) ላይ ማግኘት ይቻላል። | The latest details on the trial can be found on the Trial Tracker Blog, a site run by people close to the defendants. |
34 | እንደ የ#Freezone9bloggers የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ያሉ የኢትዮጵያ መንግስት በሰብዓዊ መብቶች ላይ የሚፈጽማቸው ጥሰቶችን ይፋ ለማውጣት የሚደረጉ ይፋዊ ጥረቶች ቀጥተኛ ያልሆነ ውጤት ነው ያላቸው። | Public attempts to highlight the Ethiopian government's transgressions against human rights such as the #Freezone9bloggers social media campaign have an indirect effect. |
35 | ለእስረኛዎቹ የተሻለ አያያዝ እንዲኖር ለማረጋገጥ የኢትዮጵያ መንግስትን ለማሳፈር ያለሙ ናቸው። | They seek to shame the Ethiopian government to ensure better treatment for the prisoners. |
36 | እንዲሁም በአለምአቀፍ ድርጅቶች እና እንደ ለኢትዮጵያ መንግስት ወሳኝ የጦር እና የደህንነት አጋር በሆነችው አሜሪካ ያሉ ተባባሪዎች ላይ ጫና ለማሳረፍም ያለሙ ናቸው። | They also seek to pressure international organizations and Ethiopia's allies such as the United States, for whom Ethiopia is a critical military and security partner. |
37 | ተስፋ የሚደረገው እነዚያ ድርጅቶች በተራቸው ኢትዮጵያ የዞን ፱ ተከሳሾችን ነጻ እንድታወጣ የፖለቲካ ጫና እንዲያሳርፉ ነው። | The hope is that those organizations will in turn apply political pressure on Ethiopia to free the Zone9 defendants. |
38 | እንግዲህ በአለምአቀፍ ደረጃ ቃል የተገባባቸውን ነገሮች መተግበር የሚወሰነው እየሰራ እና ተፈጻሚነት ባለው የህግ ስርዓት ሳይሆን በዋነኝነት በድርድር የሚካሄድ የፖለቲካ ሂደት ነው የሚመስለው። | The implementation of international commitments seems to rest primarily upon a negotiated process of politics, not a functioning and enforceable system of law. |
39 | ኢትዮጵያ ውስጥ ለፖለቲካዊ ዓላማ ሲባል ህጉ ምን ያህል በቀላሉ ስራ ላይ እንደሚውል ወይም ችላ እንደሚባል ሲታይ ጉዳዩ ለእነሱ እንዲፈታላቸው ያለው ተስፋ ፖለቲካዊ ጫና ብቻ መሆኑ ሲታይ ነገርየው ከባድ ምጸት ነው። | Considering the ease with which national law in Ethiopia is employed or ignored for political ends, it is a grim irony that only political pressure can hope to resolve the case in their favor. |