# | amh | eng |
---|
1 | ይህ የባቡር መሥመር የአቡነ ጴጥሮስንና የዐፄ ምኒሊክን ሐውልት እንዲነሡ ያደርጋል? ጊዜው 1988 ዓ. | Wiping Out Ethiopia's History for the Sake of Development |
2 | | It was in 1896 that Ethiopian forces led by Emperor Menelik II had defeated an Italian army with better contemporary military technology at the Battle of Adwa. |
3 | ም. | |
4 | ነበር፤ ጣሊያን ኢትዮጵያን በትዕቢት የወረረችበት፡፡ በወቅቱ የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት የነበሩት አጼ ምኒልክ መላውን የኢትዮጵያ ህዝብ ከጎናቸው አሰልፈው የጊዜውን ዘመናዊ መሳሪያ የታጠቀውን የጣሊያን ጦር አድዋ ላይ ድል አደረጉ፡፡ በቀሪው የንግስና ዘመናቸው ደግሞ በዘመኑ መንፈስ የተቃኙ ብዙ ስራቸውን ሲያከናወኑ የባቡር መስመርን ጨምሮ በርካታ ስልጣኔዎች ወደሀገራችን እንዲገቡ ጥረት በማድረግ አሳልፈዋል፡፡ ለዚህ የአድዋ ድልና ሀገሪቱ ዘመናዊ እንድትሆን ላደረጉት ጥረት መታሰቢያ ይሆን ዘንድ ይህ ሐውልት በመሐል አዲስ አበባ አራዳ ጊዮርጊስ ቆመላቸው፡፡ | Subsequently, the victorious Emperor had brought in a range of technologies including railway to transform his country. For his triumph at Adwa and for his endeavor to change Ethiopia in his own ways, a statue in his honor was erected at the center of Addis Ababa called Arada. |
5 | በቆራጥ ኢትየጵያውን ጽናት የተሸነፈው የጣሊያን ጦር ለአራት አስርት ዓመታት ራሱን ሲያደራጅ እና ሲያደባ ቆይቶ በ1928 ዓ. | The statute of Emperor Menelik II in Addis Ababa, Ethiopia. |
6 | ም. | Photo courtes of Abel Wabell. |
7 | ኢትዮጵያን ወረረ፡፡ ከመጀመሪያዎቹ ኢትዮጵያውን ጳጳሳት አንዱ የሆኑት ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ እጃቸውን ተይዘው ማርሻል ግራዚያኒ ፊት ቀረቡ፡፡ “የኢጣሊያ መንግስት ገዢነትን አሜን ብለህ ተቀበል” ተብለው ሲጠየቁ “የኢትየጵያ ህዝብ ለዚህ ጠላት እንዳይገዛ አውግዣለው፡፡ የኢትዮጵያ መሬት ጠላትን ብትቀበል የተረገመች ትሁን፡፡በፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም የተወገዘች ትሁን፡፡” ብለው ተናገሩ፡፡ከዚያ በማርሻል ግራዚያኒ ትእዛዝ በስምንት ጥይት ተደብድበው ወደቁ፡፡ አለመሞታቸው ሲታወቅ ከግራዚያኒ አዛዦች አንዱ በሦስት የሽጉጥ ጥይት ራሳቸውን በመምታት ገደላቸው፡፡ ይህን ለሀገር ነጻነት የከፈሉትን መስዋዕትነት ለማዘከር በግፍ ከተገደሉበት ቦታ በቅርብ ርቀት ሐውልት ተሰራላቸው፡፡ | Almost forty years later, in 1935, the Italians launched a new but a prearranged military campaign endorsed by their then belligerent leaders. The Italians managed to have a brief military occupation of Ethiopia but faced a staunch resistance from Ethiopians. |
8 | ይሁንና ከቻይናው ሪልዌይ ግሩፕ ሊሚትድ ጋር በመተባበር የከተማ ባቡር መስመር ለመዘርጋት ያቀደው የኢትዮጵያ መንግስት እነዚህን ሁለት ሐውልቶች ሊያፈርስ መዘጋጁቱ ብዙ ኢትዮጵያውያንን አስቆጥቷል፡፡ | Pope Abune Petros, who was among the first Popes of Ethiopian Orthodox Church, was the leading figure of the resistance in Ethiopia. |
9 | ስለኢትዮጵያ ታሪክ ባሕል እምነት ፖለቲካ እና ትውፊት ምልከታውን የሚያቀርበው ዳንኤል ክብረት መሠረታዊ ጥያቄውን በማስቀድም ትችቱን አስከተለ፡፡ | The Italians never liked what he was doing as a patriot and tried to stop him. |
10 | | He was forced to appear before General Rodolfo Graziani to submit and declare the Ethiopian patriots as bandits. |
11 | ይህ የባቡር መሥመር የአቡነ ጴጥሮስንና የዐፄ ምኒሊክን ሐውልት እንዲነሡ ያደርጋል? | He refused to comply with their demand and condemned the aggressors instead. |
12 | ለዚህ ጥያቄ ምላሹ ‹አዎን› ከሆነ ስለ ባቡሩ የሚኖረን ግምት ይለያል፡፡ ኢትዮጵያን እናሳድጋለን ስንል ያሳደጓትን እየዘነጋንና መታሰቢያቸውን እያፈረስን መሆን የለበትም፡፡ ‹በማን ላይ ቆመሽ እግዜርን ታሚያለሽ› አለ ያገሬ ሰው፡፡ የምናመጣው አዲስ ነገር ባለን ላይ የሚጨመር እንጂ ያለንን የሚያጠፋ መሆን የለበትም፡፡ መኪና ያስፈልገናል፣ ግን እግር የሚቆርጥ መሆን የለበትም፡፡ ወደድንም ጠላንም ይህች ሀገር የታሪክና የቅርስ ሀገር ናት፡፡ ይህ ታሪኳና ቅርሷ ደግሞ የህልውናዋም ምንጭና መሰንበቻም ጭምር ነው፡፡ ይህን ታሪክና ቅርስ እያጠፉና እያበላሹ የሚመጣ ለውጥ አንገት ቆርጦ ፀጉርን እንደማስተካከል ነው የሚቆጠረው፡፡ እናም የሚመለከታቸው ሁሉ ወደ ርምጃ ከመግባታቸው በፊት ሦስት ጊዜ ሊያስቡ ይገባል፡፡ መቼም የመጀመርያውን ባቡር ያስገቡትን የዐፄ ምኒሊክን ሐውልት አፍርሶ ባቡር እናስገባ ማለት የታሪክ ምጸት ነው፡፡ ለነጻነት የተሠውትን የአቡነ ጴጥሮስ ሐውልት ነቅሎ በባቡር ላይ በነጻነት ለመሄድ መከጀል ግፍ መሥራት ነው የሚሆነው፡፡” | |
13 | አብይ ተክለ ማርያም ደግሞ ይህ ወሬ ውሽት እንዲሆን ተመኝቷል፡፡ | He asked Ethiopians to struggle for their freedom. Finally, the Italians executed him in public. |
14 | | As it was done with Emperor Menelik II, a statue of Abune Petros was built at the center of Addis Ababa as reminiscent of his unwavering stand for his country. |
15 | አሁን በአዲስ አበባ እየተገነባ ላለው የባቡር መስመር ዋና ቲፎዞ ነኝ፡፡ ከአራት አመት በፊት ስለእርሱ ረጅም መጣጥፍ ጽፌ ነበር፡፡ ነገር ግን እጅግ ጥልቅ የዐሳብ ድህነት ያጠቃቸው የከተማችን ንድፍ ሰሪዎች መስመሩን ለመዘርጋት ከፍተኛ ዋጋ የሚሰጣቸውን ታላላቅ የታሪክ ምልክቶችን የሚዘክሩ ሁለት ሐውልቶች ለማፍረስ ወይም ቦታቸውን መቀየር አለብን ብለዋል? | However, unconfirmed reports are circulating online that the two iconic statues found on an historical thoroughfare might get wrecked due to an Addid Ababa rail tunnel construction project. The reports have not been received well by some netizens. |
16 | በፌስቡክ ያነበብካቸው አሉባልታዎች ውሸት እንዲሆኑ ተስፋ አደርጋለው፡፡ | The statute of Pope Abune Petros in Addis Ababa, Ethiopia. |
17 | ሙሴ ጌታቸው ቀጠለ፡፡ | Photo courtesy of Abel Wabell. |
18 | 1. ጧት ጉዞ ላይ ሳለሁ፤ ፋና ሬዲዮ ይፈርሳሉ ተብሎ እየተወራ ያለው የአጼ ምኒልክ እና የአቡነ ጴጥሮስ ኅውልቶች የማህበራዊ ድረ-ገጾች የሚያናፍሱት ያልተጣራ አሉባልታ እንደሆነ ነገረን። | Daniel Kiberet, a blogger who usually write on culture, history and spirituality of Ethiopia, asks [amh]: Will the Addis Ababa rail lines construction destroy the statues of Emperor Menelik II & martybishop Abune Petros? |
19 | 2. ፋና በተጨማሪ እንዳወራው አዲስ አበባ መንገዶች ሊያሰራ ባአቀደው መንገድ፦ | If the answer to this question is yes, our stance for the rail lines construction would be different! |
20 | | Our development should not come at the expense of the statues of forefathers of Ethiopia who have given their life for the country! |
21 | 1.1. የአቡነ ጴጥሮስ ኅውልት ብቻ ተነስቶ፤ መንገዱ ከተጠናቀቀ በኋላ ተመልሶ እንደሚተከል | There is a saying which says “Are you gossiping God while you give your weight for the soil!” |
22 | 1.2. የአጼ ምኒልክ ኅውልት ግን በምንም ምክንያት እንደማይነካ ነበር የነገረን። | What we put in for development should reflect on what we already have, it should not destroy what we have. |
23 | 3. አሁንም ኢህአዴግ/መንግስት ካለው ድብቅነት ያስተላለፈው መልዕክት በፍፁም አላምነውም። | We might need vehicles but the vehicles should not cut off our feet. |
24 | | Whether we like it or not Ethiopia is a country with rich history and heritage and these are foundations for our survival and continuation. |
25 | | So constructing rail lines at the cost of Ethiopia's iconic figures is like going to a barber shop for hair cut after amputating one's head! |
26 | ይህም እንደ ቀድሞዎቹ ጀግኖቻችን እና አርዓያዎቻችን የመግደል አባዜ ነው። | The project group should think thrice before they decide to demolish these statutes. |
27 | 4. የአውሮፓ የጥንት ከተሞች ላይ ያሉ ኅውልቶችም ሆኑ የቅርስ ቦታዎች በመሰረተ ግንባታ ምክንያት ሲፈርሱ ሰምቼም አይቼም አላውቅም። | Destroying a figure of a man who had built the first railway in Ethiopia a century ago to construct rail lines is a complete sarcasm! |
28 | | Demolishing the statute of a man who had given his life for freedom of his country and wishing to commute freely on the train is an indulgence. |
29 | | Abush Zekaryas relates an incident related to the recent controversy, which erupted in Italy after a small town east of Rome built a memorial to a Fascist military leader, General Rodolfo Graziani, using public funds. |
30 | ከዚህ በተቃራኒ Site Adaptation በመጠቀም ከቀድሞ ጎልተው እንዲታዩ ይደረጋሉ። | He writes [amh]: |
31 | | While some Italians built a memorial to a Fascist military leader, there is a rumor that Ethiopians are set to demolish the iconic statues of Menelik II and Abune Petros! |
32 | 5. ምናልባት ህዝቡን ለማሳመን መንግስት ይህንንም እንደሌሎቹ ልምዶች (የምርጫ የስነ-ምግባር ህግ፣…) “ከሌሎች አገሮች የቀሰምኩት ምርጥ ልምድ ነው” ማለት ነበረበት። | What an irony - this is the difference and this is the progress! And Aderegen, an anonymous group of bloggers, posted on their blog [amh]: |
33 | አንድ አድርገን የተባሉ ህቡዕ ጦማሪያን ደግሞ አስተያየታቸውም እንዲህ አስፍረዋል፡፡ | What we are asking is “Why are these kinds of projects not preplanned? |
34 | እኛ እያልን ያለነው ሀገሪቱ ላይ የሚሰሩ ፕሮጀክቶች ለምን ቅድመ ጥናት ሲካሄድ የእምነትና የሐውልት ቦታዎች ፤ የአባቶቻችን ለቤተክርስቲያንም ሆነ ለኢትዮጵያ አሻራቸውን ያስቀመጡበት ቦታ ከግምት ውስጥ አይገባም ? | Why are the statues and historical places of our forefathers who have contributed a lot for Ethiopia not given due emphasis during planning? |
35 | ወይስ ከበስተጀርባ ሌላ ነገር አለ……?.. | Or is there a conspiracy against Ethiopia's history? |
36 | | However, pro-government media, Fana Broadcasting Corporate, has a self contradictory story on their website denying the iconic statues will be demolished for rail lines construction! |
37 | ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት አ. | [amh]: |
38 | ማ በመካነ ድሩ ዜናውን አስተባብሎ እርስ በርሱ የሚጣረስ ዘገባውን አስነብቧል፡፡ | The rail lines will be contracted without doing any damage to the statues. |
39 | ሀውልቱ ምንም ችግር ሳይደርስ የባቡር መስመር ዝርጋታው ይከናወናል ያሉት ሃላፊው ፥ የባቡር መተላለፊያ ዋሻ ከሃውልቱ ስር ስለሚገነባ ፤ ግንባታው እስኪያልቅ ድረስ ሃውልቱ ለጥቂት ጊዜ ተነስቶ ከዋሻው መጠናቀቅ በኋላ ወደ ቦታው እነደሚመለስ ተናግረዋል። | However, as the Addis Ababa rail tunnel project passes through the iconic thoroughfare it will momentarily dig up the Abune Petros statue and it will not get anywhere near the statue of Menelik II. |
40 | አያይዘውም ይህ የባቡር መስመር ግንባታ የዳግማዊ ሚኒሊክ ሀውልትን በምንም መልኩ እንደማይነካው የሚወራው ወሬ መሰረተ ቢስ መሆኑንም ነው ያስረዱት።” | All the rumors revolving around this are baseless. This is the second time in a year that the Ethiopian government has sparked controversy involving a statue. |
41 | መንግስት በሐውልቶች ምክንያት ከህዝቡ ከፍተኛ ተቃውሞ ሲገጥመው ይህ የመጀመሪያው አይደለም፡፡ ከዚህ በፊት በቻይና መንግስት በተገነባው የአፍሪካ ህብረት አዳራሽ ቅፅር ግቢ ውስጥ የአፍሪካ አባት ተብለው የሚጠሩት ቀዳማዊ አጼ ኃይለ ሥላሴን በመተው ለጋናዊው ክዋሜ ንክሩማህ መሰራቱ ብዙዎችን እንዳስከፋ የሚታወስ ነው፡፡ | Kwame Nkrumah's statue, which was unveiled at the African Union (AU) headquarters, which was built with help of the Chinese government, has also sparked anger amongst Ethiopians as many Ethiopians feel that the country's former leader Haile Selassie also deserved recognition. |