# | amh | eng |
---|
1 | ኢትዮጵያውያን #SomeoneTellSaudiArabia በሚል ስደተኞች ላይ የደረሰውን እርምጃ ተቃወሙ | Ethiopians: #SomeoneTellSaudiArabia to Stop Immigration Crackdown |
2 | ጥቅምት 25፣ 2005 ሳኡዲ አረቢያ በሕገወጥ ስደተኞች ላይ እርምጃ መውሰድ ጀመረች፡፡ ሳኡዲአረቢያ 7 ሚሊዮን የሚሆኑ የውጭ ዜጋ ሠራተኞች እና ቤተሰቦቻቸውን አስጠልላለች ተብሎ ይታመናል፡፡ የሳኡዲ አረቢያ መንግሥት ለሕገወጥ ስደተኞች የዘጠኝ ወር የእፎይታ (amnesty) ጊዜ በሚያዝያ ወር 2005 ሕጋዊ ዕውቅና እንዲያገኙ አሊያም አገሪቷን እንዲለቁ ሰጥቶ ነበር፡፡ | On November 4, 2013, Saudi Arabia began enforcing a crackdown on illegal immigrants. Saudi Arabia is believed to be home to more than seven million foreign workers and their families. |
3 | ከሰሃራ በታች የምትገኘዋ የኢትዮጵያ ስደተኞች በዚህ የመንግሥት እርምጃ በፅኑ ከተቸገሩት ውስጥ ይመደባሉ፣ ይህም ዓመፅ እና ብጥብጥ አስከትሏል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት በሳኡዲአረቢያ በሕገወጥ መንገድ የሚኖሩትን ሰዎች በሳኡዲ ፖሊሶች አንድ ኢትዮጵያዊ መገደሉ ከተነገረ በኋላ ወደአገራቸው መመለስ ጀምሯል፡፡ | The Saudi government issued an amnesty period in April 2013 giving illegal immigrants seven months to gain legal status or leave the country. Immigrants from Ethiopia, a Sub-Saharan African country, are one of the most affected by the crackdown, which has resulted in riots and violence. |
4 | በተለያዩ የዜና እና የማኅበራዊ አውታሮች እንደተገለጸው ከሆነ የኢትዮጵያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቴድሮስ አድሃኖም የሳኡዲ አረቢያን ሕገወጥ ስደተኞችን የማስወጣት መብት ቢያምኑም የኃይል አጠቃቀማቸው እና ሴቶች ላይ የደረሰው የመድፈር ድርጊትን አውግዘዋል፡፡ | The Ethiopian government is repatriating its citizens living in Saudi Arabia illegally after it was reported that an Ethiopian was killed by Saudi police. |
5 | | The Minister of Foreign Affairs in Ethiopia Tedros Adhanom acknowledged the right of Saudi Arabia to expel illegal immigrants but condemned the use of force and rape against Ethiopian immigrants as it has been reported on different news and social media sites. |
6 | ከታች የሚታየው ቪዲዮ በአምሃሪክትዩብ የተለጠፈ ሲሆን ከሳኡዲ አረቢያ የሕገወጥ ስደተኞችን መመለስ ያሳያል፡- | Below is a video posted on YouTube by user Amharictube showing mass exodus of immigrants in Saudi Arabia: |
7 | MoveOn.org የተባለ ድረገጽ ላይ ፊርማ የማሰባሰብ ሥራ የተጀመረ ሲሆን ለተባበሩት መንግሥታት እና እንደ አምነስቲ ኢንተርናሽናል ላሉ የሰብኣዊ መብቶች ድርጅቶች በሳኡዲ አረቢያ ስለኢትዮጵያውያን ስደተኞች አያያዝ ለማሳወቅ ታቅዷል፡፡ | A petition has been created on MoveOn.org to alert the United Nations and human rights organizations such as Amnesty International about the plight of Ethiopian immigrants in Saudi Arabia. |
8 | ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች በበይነመረብ #SomeoneTellSaudiArabia የሚል ኃይለ ቃል በመጠቀም በሳኡዲ አረቢያ ያለውን የኢትዮጵያውያን ስደተኞችን አያያዝ አውግዘዋል፡፡ | Ethiopians and friends of Ethiopia online have been using the hashtag #SomeoneTellSaudiArabia to condemn the treatment of Ethiopian immigrants in Saudi Arabia. |
9 | ማሕሌት (@Mahlet_S) ስደተኞች ወንጀለኞች ሳይሆኑ ሥራ ፈላጊዎች መሆናቸውን አስታውሳለች፡- | Mahlet (@Mahlet_S) noted that immigrants are not criminals but job seekers: |
10 | #SomeoneTellSaudiArabia ስደተኞች አገራቸው የገቡት ሥራ ፍለጋ እና ለእንጀራ እንጂ ወንጀለኛ አለመሆናቸውን ለሳኡዲአረቢያ ሊነገራት ይገባል፡፡ | #SomeoneTellSaudiArabia that immigrants are in their country only looking for jobs and make a living, they are not criminals. |
11 | - Mahlet (@Mahlet_S) November 11, 2013 | - Mahlet (@Mahlet_S) November 11, 2013 |
12 | አዲስ ስታንዳርደ (@addisstandard) የተሰኘ ወርሓዊ የኢትዮጵያ መጽሔት ደግሞ፡- | Addis Standard (@addisstandard), a monthly magazine in Ethiopia, wrote: |
13 | #SomeoneTellSaudiArabia ሰው መሆን ማለት ምን ማለት እንደሆነ ለመረዳት ከሃይማኖታዊ ቀናተኛነት ይልቅ ሰብኣዊ ሞራል ይጠይቃል፡፡ | #SomeoneTellSaudiArabia it takes human moral not religious zealotry to understand what it means to be human! |
14 | - Addis Standard (@addisstandard) November 12, 2013 | - Addis Standard (@addisstandard) November 12, 2013 |
15 | አንዳንዶች ደግሞ በኢትዮጵያ እና ኢስላም መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት አስታውሰዋል፡፡ ሐፍሳ መሐመድ (@hafsamohamed1) የሚከተለውን ጠቁሟል፡- | Some users revisited the historical relationship between Islam and Ethiopia. Hafsa Mohamed (@hafsamohamed1) pointed out that: |
16 | #SomeoneTellSaudiArabia ነብዩ መሐመድ (ሰዐወ)ተከታዮቻቸው ኢትዮጵያን እንዳያስከፉ ተናግረዋል፡፡ እነርሱ ግን ዘነጉት፡፡ #Ethiopia. pic.twitter.com/XxZocICmPr | #SomeoneTellSaudiArabia Prophet Mohammad (PBUH) [Peace Be Upon Him] ordered his followers never to provoke/wrong #Ethiopia. They Forgot. pic.twitter.com/XxZocICmPr |
17 | - Hafsa Mohamed (@hafsamohamed1) November 12, 2013 | - Hafsa Mohamed (@hafsamohamed1) November 12, 2013 |
18 | ካሊ (@KaliDaisyy) የጻፈው:- | Kali (@KaliDaisyy) wrote: |
19 | #SomeoneTellSaudiArabia ኢትዮጵያ ከመካ ለመጡት እና በቁራይሽ ጎሳ ለተከሰሱት የሙስሊም ስደተኞች እጆቿን ዘርግታ ነበር፤ እና አሁን እነርሱ ይገድሉናል? | #SomeoneTellSaudiArabia Ethiopia had opened her hands to the Muslim immigrants from Mecca, persecuted by Quraysh tribe & now they kill us? |
20 | - Kali (@KaliDaisyy) November 12, 2013 | - Kali (@KaliDaisyy) November 12, 2013 |
21 | የሥነ ልቦና ባለሙያው አንቶኒዮ ሙላቱ (@AntonZfirst) በነብዩ መሐመድ ስለኢትዮጵያ የተሰጠውን ምክር ማጣቀስ መርጧል፡- | Pschologist Antonio Mulatu (@AntonZfirst) referred to advice given by Prophet Muhammad about Ethiopia: |
22 | 1/ #SomeonetellSaudiArabia ነብዩ መሐመድ እንዳሉት ‹‹ከፈለጋችሁ ወደኢትዮጵያ ሂዱ፡፡ እዚያ ማንንም የማይጎዳ ንጉሥ አለ፡፡›› | 1/ #SomeonetellSaudiArabia prophet #Mohammed said “Go to #Ethiopia if you wish. |
23 | - Antonio Mulatu (@AntonZfirst) November 12, 2013 | There is a ruler who does not torment anyone. |
24 | በኢትዮጵያ እና በሙስሊሞች መካከል ያለው ግንኙነት የሚጀምረው ኢትዮጵያ በመካ ገዢዎች ተሰደው ለመጡት ሙስሊሞች ሠላማዊ መሸሸጊያ ስትሰጥ ነው፡፡ ቢላል ኢብን አል ሐበሽ ከቀደምት የመሐመድ ተከታዮች አንዱ እና የመጀመሪያ ሙኧዚን (የአዛን ዜማ አሰሚ) ሲሆን ኢትዮጵያዊ ነው፡፡ | - Antonio Mulatu (@AntonZfirst) November 12, 2013 The relatonship between Ethiopia and Muslim dates back to the time when Ethiopia provided a safe haven to Muslims who were fleeing persecution from the rulers of Mecca. |
25 | በኢስላም አራተኛ ቅዱስ ከተማ የምትባለዋ ሐረር ከተማ በኢትዮጵያ ነው የምትገኘው፤ 82 መስኪዶች፣ ሦስቱ ከ10ኛው ክፍለዘመን ጀምሮ ያሉ ሲሆን 102 መስገጃዎችም አሏት፡፡ | Bilal ibn Rabah al-Habash, one of the foremost companions of Muhammad and the first Muezzin, the person who recites the call to prayer, was Ethiopian. |
26 | | Ethiopia is home to Harar, which is considered the fourth holy city of Islam, with 82 mosques, three of which date from the 10th century, and 102 shrines. |
27 | ኢትዮጵያ ከዚህም በተጨማሪ በእስልምና ታሪክ የመጀመሪያው ሒጅራ (የሙስሊሞች ስደት ከክስ ሽሽት) የተካሄደባት አገር ናት፡፡ | Ethiopia is also the site of the First Hijrah, the migration of Muslims to escape persecution, in the history of Islam. |
28 | በሌላ በኩል አኑፍ (@anoofesh) ከሪያድ፣ ሳኡዲ አረቢያ የኢትዮጵያዊ ስደተኞች በሳኡዲ አረቢያ እና የያኔዎቹ የሳኡዲ አረቢያ እና ሙስሊም ስደተኞች በኢትዮጵያ መካከል ያለውን ልዩነት በተመለከተ ልዩነቱን ተናግሯል፡- | However, anoof (@anoofesh) from Riyadh, Saudi Arabia, disagreed with the comparison between Ethiopia immigrants in Saudi Arabia and Muslim immigrants in Ethiopia: |
29 | @KaliDaisyy ሙስሊሞች ስደተኞች ግን ኢትዮጵያ ውስጥ የነበሩት በሕገ ወጥ መንገድ አልነበረም | @KaliDaisyy The muslim immigrants were not in Ethiopia illegally :) |
30 | - anoof (@anoofesh) November 12, 2013 | - anoof (@anoofesh) November 12, 2013 |
31 | መላክ መኮንን (@melak_m) ያንን በተመለከተ፡- | Melak Mekonen (@melak_m) observed that: |
32 | #SomeoneTellSaudiArabia: ሕገ ወጥ ስደትን መከላከል ይቻላል፤ ነገር ግን በመደብደብ፣ በመግደልና በማሰር አይደለም! | #SomeoneTellSaudiArabia :You have a right to address irregular migration, but not to abuse, kill, persecute! |
33 | - Melak Mekonen (@melak_m) November 12, 2013 | - Melak Mekonen (@melak_m) November 12, 2013 |
34 | የእንግሊዙ ሪስፔክት ፓርቲ ሊ ጃስፐር (@LeeJasper) ደግሞ የኢትዮጵያውያን ስደተኞቹን ጉዳይ በእስራኤል ይዞታ ካሉት ፍልስጤማውያን ጋር አነጻጽራዋለች፡- | Lee Jasper (@LeeJasper), a member of Respect Party in the UK, saw the plight of Ethiopian immigrants similar to that of Palestinians under Israeli occupation: |
35 | #SomeoneTellSaudiArabia that their racist treatment of #Ethiopians is in many ways just as bad as #Israeli treatment of #Palestinians. | #SomeoneTellSaudiArabia that their racist treatment of #Ethiopians is in many ways just as bad as #Israeli treatment of #Palestinians. |
36 | - Lee Jasper (@LeeJasper) November 12, 2013 | - Lee Jasper (@LeeJasper) November 12, 2013 جبرتينهو (@iabj) opined: |
37 | #SomeoneTellSaudiArabia የውጭ ዜጎች ባርያዎች አይደሉም፣ ድህነትም እንከን አይደለም፡ | #SomeoneTellSaudiArabia Foreigners are not slaves and that poverty is not a defect |
38 | - جبرتينهو (@iabj) November 12, 2013 | - جبرتينهو (@iabj) November 12, 2013 |
39 | በጄኔቫ፣ ስዊዘርላንድ የሰብኣዊ መብት ባለሙያው ይሄነው ዋለልኝ (@YeheneWalilegne) የሳኡዲ አረቢያን ለተባበሩት መንግሥታት የሰብኣዊ መብት ቆንስላ እጩ ሆና መቅረብ ተቃውሟል፡- | Ethiopian human rights specialist based in Geneva, Switzerland, Yehenew Walilegne (@YeheneWalilegne) opposed Saudi Arabia's candidacy to the United Nations Human Rights Council: |
40 | #SomeoneTellSaudiArabia #UNGA የተባበሩት መንግሥታት የሳኡዲ አረቢያን የሰብኣዊ መብት ቆንስላው ሆና መታጨት ውድቅ ሊያደርጉት ይገባል፡፡ አለዚያ የመንግሥታቱ እና የቆንስላው ታማኝነት ጥያቄ ውስጥ ይወድቃል፡፡ | #SomeoneTellSaudiArabia #UNGA shld reject #KSA‘s candidacy 2 become member of z #Human Rights Council. #UNGA & #HRC credibility is at stake |
41 | - Yehenew Walilegne (@YeheneWalilegne) November 12, 2013 | - Yehenew Walilegne (@YeheneWalilegne) November 12, 2013 |
42 | ሕዳር 3፣ 2006 ግን ሳኡዲ አረቢያ፣ ቻይና፣ ራሺያ እና ኩባ የሰብኣዊ መብት ቆንስላውን መቀመጫዎች ማሸነፍ ችለዋል፡ | Saudi Arabia, China, Russia and Cuba won seats on the United Nations Human Rights Council on Tuesday, November 12, 2013. |
43 | አኑፍም ለኢትዮጵያውያን እንዲህ ብሏል፡- | anoof told Ethiopians: |
44 | @KaliDaisyy ምን ያህል ክፉ እንደሆንን እና እንደተበሳጫችሁብን ልትነግሩን ብቻ ትፈልጋላችሁ፡፡ ብዙዎቻችሁ ምን እየተካሄደ እንደሆነ እንኳን አታውቁም፡፡ #SomeoneTellSaudiArabia | @KaliDaisyy You just want to call us evil and tell us how upset you are. Most of you have no idea whats going on. |
45 | - anoof (@anoofesh) November 12, 2013 | #SomeoneTellSaudiArabia - anoof (@anoofesh) November 12, 2013 |